በአከባበሩ ስነስርዓት ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልቃድር እንዲሁም አቶ ጃንጥራር አባይ የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባና የስራ ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ሀላፊ እንዲሁም ሌሎች የምክር ቤቱና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና ሰራተኞች ተገኝተዋል።
አቶ ጃንጥራር አባይ በዚሁ ስነስርዓት ላይ ከተናገሩት :-
👉 “ዜጎች ለሀገራቸው ያላቸው ፍቅርና ብሔራዊ ስሜት ለሰንደቅ ዓላማ በሚሰጡት ክብር ይገለጻል፡፡
👉 እኛ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ለሰንድቅ ዓላማ የምንሰጠው ፍቅርና ክብር ከናት ካባቶቻችን በክብር የወረስነው ለቀጣዩ ትውልድ በክብር የምናወርሰው በልባችን ውስጥ ታትሞ የሚቆይ የብዝሀነታችንና የአንድነታችን የሉዓላዊነታችን መገለጫ ታላቅ ሀገራዊ ዕሴት ነው፡፡
👉 ሰንደቅ ዓላማችን የግዛት አንድነት ፣ የአብሮነት የብሔራዊ መግባባት መገለጫ ዓርማችን በመሆኑ ማንኛውም ዜጋ ለሰንደቅ ዓላማ ክብር መስጠት የማክበርና የማስከበር ኃላፊነት አለበት ፡፡
👉 የውስጥ ቅጥረኞችና ተላላኪዎቻቸው ብሔራዊ አንድነታችንን ሉዓላዊነታችንን አደጋ ላይ ለመጣል እየሰሩ ባለበት በዚህ ወቅት ሰንደቅ ዓላማ ቀን መከበሩ ለሕበረ ብሄራዊ አንድነታችን መጠናከርና መነቃቃት ትልቅ ትርጉም አለው
👉 በዓሉን ስናከብር ለሀገር ሉዓላዊነትና ጥቅም መከበር ዳግም ቃልኪዳንናችንን የምናድስበት ነው
ባንዲራችንየህዝባችን የደም ውጤት ነው፡፡
👉 ዛሬም ለባንዲራችን ድሙን እያፈሰሰ ያለው የሀገራችን መከታ ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን በዓላችንን በድምቀት እንድናከከብር አድርገውናልና እናመሰግናቸዋለን!
👉 በኢትዮጵያዊ አንድነታችን ጸንተን የተጋረጠብንን አደጋ በጋራ በመመከት የሀገራችንን ሕልውና ላለማስደፈር በየትኛውም ጊዜ መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ሆነን ባንዲራችንን ከፍ አድርገን የምንሰቅል በአንድንት ቆመን ለጠላት የማንበገር ኢትዮጵያውያን ነን፡፡