👉 መንገድ መሰረተ ልማት በተመለከተ
 በከተማችን የመጀመሪያ የሆነውና ረጅም የመሬት ውስጥ ዋሻ ያካተተ በ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተሰራው የፑሽኪን ጎተራ መንገድ
 በ2015 የመጀመሪያው ሩብ አመት ውስጥ 8.35 ኪ.ሜትር የመንገድ ግንባታ እና 181.4 ኪ.ሜትር የጥገና ስራዎች ለማከናወን ታቅዶ በቅደም ተከተል 20.12 (240.9%) ኪ.ሜትር የግንባታና 195.96 (108%) የጥገና ስራዎች ማከናወን ችሏል፡፡
 በተጨማሪም የ2577 የመንገድ መብራት አምፖል ጥገና ስራም፤ 180 ትራንስፎርመር ተከላ፤ 107.8 ኪ.ሜ አዲስ ደንበኞች መስመር ዝርጋታ እና 126.90 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር የመልሶ ግንባታ ስራ መስራት ተችሏል፡፡
 ከአዲስ የመንገድ ግንባታ ስራ ጋር በተያያዘ በበጀት አመቱ በ3 ቢሊዮን ብር በጀት 3 ግዙፍ የመንገድ ልማት ስራ ለማከናወን አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ ተከናውኗል
👉 ንፁህ መጠጥ ውሃን ተደራሽ ለማድረግ
 በ2015 በጀት ዓመት በቀን ውሃ የማምረት አቅምን ከ804 ሺህ ሜ.ኩብ ወደ 811 ሺህ ሜ.ኩብ ለማድረስ ግብ ይዘን የመጀመሪያ ሩብ አመት በከተማው ኪስ ቦታዎች ላይ 10 የውሀ ጉድጓዶች ቁፋሮ ተጠናቀዋል ::
 10 ሩንም ወደ ስርጭት ለማስገባት እንዲቻል የሚያስፈልጉ የመስመር ዝርጋታና ሌሎች ቀሪ 31 የውሃ ጉድጓድ ቁፍሮ ስራዎች በመሰራት ላይ ይገኛሉ፡፡
 የገርቢ ፕሮጀክትን ማስጀመርና ሌሎች አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በመስራት በከተማችን የሚታየውን የውሃ አቅርቦት ሽፍን ለማሳደግ በልዩ ሁኔታ እየተሰራ ነው ::
👉 ትምህርትን በተመለከተ
v በሩብ ዓመቱ የተማሪ ቅበላን ከነበረበት 1,034,373 ወደ 1,050,351 (100.42%) ደርሷል፡፡
v የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራሙና ዩኒፎርም ተጠቃሚነት ሽፋን ከ628,000 ወደ 708,265 በማሳደግ ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ በዕቅዱ እየተሰራ ነው
v አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት በማድረግ በራስ አቅም የመጸሃፍት ዝግጅት ተጠናቆ ተደራሽ የማድረግ ሥራ እየተከነሆነ ነው፡፡
v የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተደራሽነትን ከማሳደግ 24,289 (94.9%) ሰልጣኞችን በመቀበል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡
👉 አዲስ ስራ እድል ፈጠራ
v በ2015 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ለ36,039 የስራ እድል መፍጠር ተችሏል፡፡
ገቢን በተመለከተ
v በሩብ ዓመቱ 16.01 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ ተችሏል።
v የታክስ ገቢ 14.78 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ 104.97% ማሳካት ተችሏል፡፡