
ከተማ አስተዳደራችን የጥምቀት በዓልን ውበትና ድምቀቱን በመጎናፀፍ ነዋሪዎቿ በጋራ ተሰባስበው የሚያሳልፉበት በርካታ የውጪ ቱሪስቶችን የምታስተናግድበት ፤በሁሉም አቅጣጫ እንደ አበባ ፈክታ ገፅታዋም የሚገነባበት በመሆኑ አስተዳደራችን የበዓሉ ዋና እሴት የሆነውን ትህትና አገልጋይነትን በመላበስ በዓሉ በሰላም ፤በፍቅር በአብሮነት እንዲከበር የእምነቱ አባቶች ከሆኑት ከአገልጋዮቿ ጋር በቅርበት ሲሰራ ቆይቷል፡፡