በ2015 በጀት ዓመት የተሻለ ስራ ለመስራት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑን ከንቲባ አዳነች ገልፀዋል።
በሪፖርታቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፤ (በሰላምና ፀጥታ በተመለከተ ያነሱት )
👉 በሰላም፤ አብሮነትና ወንድማማችነት/ እህትማማችነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዩች ውጤታማ ሥራዎች መሠራታቸውን
👉 ጠላት አዲስ አበባን ሌላው ዋነኛው ግንባር በማድረግ ህዝባዊና የሃይማኖት በዓላትን ለማወክ ከፍተኛ ዝግጅት ቢያደርግም መዋቅራችንን፣ መላ ህዝባችንን፣ የፀጥታ ሃይሉንና የተለያዩ አደረጃጀቶችን አቀናጅተን በመምራታችን የጠላትን እቅድ ማክሸፍ መቻሉን
👉 1.5 ሚሊዩን ህዝባችን አካባቢውን እንደጠብቅ በማነቃነቅና በማደራጀት የሰላም ሰራዊቱ፤ የደንብ ማስከበር፤ የፖሊስ ሃይላችን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር የከተማችንን ሰላምና ጸጥታ ማስፈን መቻሉ
👉 ከወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ አኳያ በቀጣይም የሀገር ሉዓላዊነትና ግዛት አንድነት ለማረጋገጥ የሚያግዝ የደጀንነት ስራችንን በማጠናር ለሶስተኛ ዙር 486.2 ሚሊዮን ብር የሚገምት የገንዘብና የአይነት ድጋፍ መደረጉን :
የአስተዳደር ወሰንን በተመለከተ፥
👉 ለዘመናት የተንከባለለና ሳይቋጭ የግጭት፤ መፈናቀልና የፖለቲካ አጀንዳ ሆኖ የኖረው የአዲስ አበባ እና አጎራባች ፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የአስተዳደር ወሰን ህገ-መንግስቱንና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጋራ በተቋቋሙ ኮሚቴዎች እና በፌዴራል መንግስት የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እልባት በመስጠት ታሪካዊና ውጤታማ ስራ መስራት ተችሏል፡፡