ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ለአፍሪካ ህብረት የልማት ኤጀንሲ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ናርዶስ የሃገሪቱን የለውጥ እንቅስቃሴ በተለይም በመዲናዋ አዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ የለውጥና የሪፎርም ስራዎች ስላሉበት ደረጃ ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡
በተለይም በፈተናዎች ውስጥ አልፎ በርካታ የዜጎችን ህይወት የሚቀይር ፤ የከተማችንን ጎስቋላ ገፅታ የሚያድስ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ወ/ሮ ናርዶስ በቀለ በበኩላቸው በሃገሪቱ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ እንቅስቃሴ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልፀው በተመለከቱት ነገር በእጅጉ መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡
ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች ዘመናዊ የጥቁር ህዝቦች ኩራት መታሰቢያ የሆነውን የአድዋ ሙዚየምና የማዘጋጃ ቤት ህንፃ እድሳት ስራን ለወ/ሮ ናርዶስ አስጎብኝተዋል፡፡