ይህ አለም አቀፍ የጥፋተኞች አያያዝ መስፈርትን ያሟላና ወጣቶች ስራ ወዳድነትን እንዲሁም የስፖርትና የመዝናኛ ለወጣቶቹ ሁለንተናዊ ግንባታ የሚያግዙ ጉዳዮች የተካተቱበት ማእከል ግንባታ ከተማ አስተዳደሩ በፍጥነት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለፍሬ በቅቷል፡፡
✍️ 20,186.42 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ አርፏል
✍️6,000 ካሬ ሜትር ቦታ በአረንጓዴ ቦታ ተሸፍኗል
✍️2,892 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የከተማ ግብርና ስራ ተሰርቶበታል
✍️4364.53 ካሬ ሜትር ቦታ በውስጥ ለውስጥ የኮብልስቶን ንጣፍ ተሸፍኗል
✍️በአጠቃላይ 1,213.38 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፉ 2 የወንዶችና የሴቶች ስፖርት ሜዳዎች ተሰርተውለታል
✍️ፕሮጀክቱ አጠቃላይ 17 ብሎኮች ሲኖሩት የአስተዳደር ህንፃ፣የመማሪያ ክፍሎች፣ቤተ መፅሐፍት፣መመገቢና ማብሰያ ክፍሎች፣ክሊኒክና የምክር አገልግሎት መስጫ ክፍል፣ዎርክሾፕ፣የጠያዎች ማረፊያ፣3 የወንዶችና 2 የሴቶች ዶርሚተሪ፣ላውንደሪ፣ሁለገብ አዳራሽ እና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች ተሟልተውለታል፡፡
እንኳን ደስ አለን!!