የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይፋ ያደረጋቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች እውነታዎች፡-
👉 ሁለቱ ሜጋ ፕሮጀክቶች በጠቅላላው 7.6 ቢሊዮን ብር በሆነ ወጪ የሚሰሩ ይሆናል፡፡
👉 የመጀመርያው የግብርና ምርት ማቅረቢያና መሸጫ ማእከል በ6 ቢሊዮን በላይ በሆነ ወጪ በተለያዩ ሶስት ቦታዎች (በለሚ ኩራ ክ/ከተማ 2 ፕሮጀክትና ፤ በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ አንድ ፕሮጀክት) የሚገነቡ ይሆናል
👉 ለሚ – ኩራ ክፍለ ከተማ በወረዳ 02 በ3.88 ሄክታር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 በ2.8 ሄክታር በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 በ2.12 ሄክታር የሚያርፉ ናቸው።
👉 ፕሮጀክቱ በከተማችን አስተማማኝ የግብርና ምርት አቅርቦት እንዲኖር የሚያግዝና ገበያውን በማረጋጋት ለአምራቹም ለተጠቃሚውም ተመጣጣኝ ምርቶች እንዲቀርብ የሚያደርግ ነው፡፡
👉 ኦቪድ ግሩፕ የተሰኘው ድርጅት በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም የሚገነባው ፕሮጀክት ነው፡፡
👉 በፕሮጀክቱ የተካተቱ ነገሮችን በተመለከተ ፡- መደብሮች ፤ የጅምላ እና የችርቻሮ ገበያ አካባቢ፤ ሱፐርማርኬት፤ የቢሮ ብሎክ ለአስተዳደር፤ መጸዳጃ ቤቶች እና መገልገያዎች፤ የመግቢያ መንገድ እና የመኪና ማቆሚያ ፤ ዘመናዊ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ስርዓት ይዟል፡፡
👉 የፕሮጀክት ማጠናቀቂያ ጊዜ 6 ወራት ነው ።
👉 ሁለተኛው በ1.5 ቢሊዮን በሆነ ወጪ የሚገነባው የዘውዲቱ ሆስፒታል ማስፋፍያ የB+G+8 ፕሮጀክት ግንባታ ነው፡፡
👉 ይህ ግንባታ በርካታ ገፅታዎች ያሉት ሲሆን – ለተኝቶ ታካሚ =200 አልጋዎች – ለድንገተኛ =27 ክፍሎች- 125 መጸዳጃ ቤቶች- የቀዶ ጥገና ማዕከል – አንድ የፊዚዮቴራፒ ማዕከል – የኢሜጂንግ ማዕከል – ላቦራቶሪ – – የልጆች እና ጎልማሶች ICU ማዕከል – የነርሲንግ ጣቢያ- የስብሰባ አዳራሽ ይኖሩታል፡፡
👉 ተቋራጭ ዮሃንስ ሀይሌ ኮንትራክተር ሲሆን አማካሪ ሲጎር አማካሪ ነው።
👉 የፕሮጀክት ቆይታ ደግሞ 18 ወራት የፕሮጀክት ወጪ 1.5 ቢሊዮን ብር ገደማ ነው፡፡