ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በትናንትናው እለት ለ22ቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታዎችን እንዲሁም ለሌሎች ሁለት ተቋማት ኮሚሽነሮችን ሾመዋል፡፡
ከተሿሚዎቹ መካከል የተፎካካሪ ፓርቲ አመራር አካላት የተካተቱ ሲሆን ከእናት ፓርቲ ወ/ሮ ጥሩማር አባተ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም ከነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ወ/ሮ ነብያ መሃመድ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሹመዋል፡፡
1. ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር – አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን – የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
2. ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር – አምባሳደር ብርቱካን አያኖ – የኃብት ማኔጅመንትና አገልግሎት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
3. ገንዘብ ሚኒስቴር – ዶ/ር እዮብ ተካልኝ – የፊሲካል ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
4. ገንዘብ ሚኒስቴር – ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰዉ – የኢኮኖሚ ትብብር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
5. መከላከያ ሚኒስቴር – ዶ/ር አህመድን መሐመድ – የኮንስትራክሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
6. መከላከያ ሚኒስቴር – ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ – የፋይናንስ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
7. ግብርና ሚኒስቴር – ዶ/ር መለሰ መኮንን – የእርሻና ሆልቲካልቸር ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
8. ግብርና ሚኒስቴር – ዶ/ር ፍቅሩ ረጋሳ – የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
9. ግብርና ሚኒስቴር – ፕሮፈሰር እያሱ ኤልያስ – የተፈጥሮ ሃብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
10. ግብርና ሚኒስቴር – ዶ/ር ሶፊያ ካሳ – የግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
11. ሠላም ሚኒስቴር – አቶ ታዬ ደንደአ – ሚኒስትር ዴኤታ
12. ሠላም ሚኒስቴር – ዶ/ር ስዩም መስፍን – ሚኒስትር ዴኤታ
13. ፍትህ ሚኒስቴር – አቶ አለምአንተ አግደዉ – የመንግስት ህግና ፍትህ አገልግሎት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
14. በፍትህ ሚኒስቴር – አቶ ፍቃዱ ፀጋ – የጠቅላይ አቃቤ ህግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
15. ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር – አቶ ዳንጌ ቦሩ – የንግድ ትስስርና ውጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
16. ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር – አቶ ሐሰን መሀመድ ሙአሊን – የንግድ ስርዓትና ላይሰንሲንግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
17. ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር – አቶ እንዳለዉ መኮንን – የጥራት መሠረተ ልማትና ማረጋገጫ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
18. ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር – አቶ ሽሰማ ገ/ስላሴ – የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
19. ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር – አቶ ታረቀኝ ቡልቡልታ – የዕድገትና ተወዳዳሪነት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
20. ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር – ዶ/ር ባይሳ በዳዳ – የምርምርና ኢኖቬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
21. ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር – ወ/ሮ ሁሪያ አሊ – የአይሲቲና ዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
22. ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር – ዶ/ር አብረሃ አዱኛ – የዉሃ ሃብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
23. ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር – ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋቅሻዉ – የመጠጥ ዉሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
24. ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር – ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ – የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
25. ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር – አቶ ፈንታ ደጀን – የከተማ አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
26. ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር – አቶ ሄኖስ ወርቁ – የቤቶችና ከተማ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
27. ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር – አቶ ካሊድ አብዱራሂማን – የመሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
28. ማዕድን ሚኒስቴር – አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ – የማዕድን ነዳጅ ልማትና ቁጥጥር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
29. ማዕድን ሚኒስቴር – አቶ ቶማስ ቱት – የጂኦ ሳይንስና ምርምር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
30. ጤና ሚኒስቴር – ዶ/ር ደረጄ ድጉማ – የአገልግሎትና ፕሮግራም ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
31. ጤና ሚኒስቴር – ወ/ሮ ሰሀርላ አብዱላሂ – የኃብትና ግብአት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
32. ጤና ሚኒስቴር – ዶ/ር አየለ ተሾመ – የሥርዓት አቅም ግንባታ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
33. ትምህርት ሚኒስቴር – ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ – የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
34. ትምህርት ሚኒስቴር – ዶ/ር ፈንታ ማንደፍሮ – የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
35. ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር – አቶ ካሳሁን ጎፌ – የመሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
36. በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር – አቶ በረኦ ሐሰን በረኦ – የአገልግሎትና ቁጥጥር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
37. ቱሪዝም ሚኒስቴር – አቶ ስለሺ ግርማ – የቱሪዝም መዳረሻና መሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
38. ቱሪዝም ሚኒስቴር – ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት – የቱሪዝም ፕሮሞሽንና ግብይት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
39. ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር – ወ/ሮ አየለች እሸቴ – የማህበራዊ ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
40. ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር – ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ – የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
41. ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር – ወ/ሮ ሙና አሕመድ – የወጣቶች ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
42. ገቢዎች ሚኒስቴር – አቶ ተስፋዬ ቱሉ – የታክስ ሥርዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
43. ገቢዎች ሚኒስቴር – ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ – የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
44. ፕላንና ልማት ሚኒስቴር – ወ/ሮ ጥሩማር አባተ አያሌዉ – የክትትልና ግምገማ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
45. ፕላንና ልማት ሚኒስቴር – ዶ/ር ነመራ ማሞ – የፕላን ስታቲስቲክስ እና ፖሊሲ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
46. ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር – ዶ/ር በከር ሻሌ – የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
47. ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር – አቶ አሰግድ ጌታቸዉ – የሠራተኛ ጉዳይ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
48. ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር – አቶ ንጉሱ ጥላሁን – የሥራና የሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
49. ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር – ወ/ሮ ነብያ መሀመድ – አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ
50. መስኖና ቆላማ አከባቢ ሚኒስቴር – ዶ/ር እንድሪያስ ጌታ – የቆላማ አከባቢ ምርምርና ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
51. መስኖና ቆላማ አከባቢ ሚኒስቴር – ዶ/ር ብርሃኑ ሌንጂሶ – የመስኖ ልማት ፕሮጀክት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
52. ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር – ወ/ሮ ወርቅነሽ ብሩ – የባሕልና ቋንቋ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
53. ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር – ወ/ሮ ነፊሳ አልማሂዲ – የኪነጥበብና ስነጥበብ የፈጠራ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
54. ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር – አምባሳደር መስፍን ቸርነት – የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
55. ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት – አቶ ተስፋዬ ዳባ – የካቢኔ ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
56. ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት – ወ/ሮ አለምፀሐይ ጳዉሎስ – የአገልግሎቶችና መልካም አስተዳደር ክትትል ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ
57. ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት – አቶ ወርቁ ጓንጉል – የሀገራዊ ፕሮጀክቶች ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ
58. የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት – አቶ ከበደ ደሲሣ – ሚኒስትር ዴኤታ
59. የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት – ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ – ሚኒስትር ዴኤታ
60. የፌደራል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን – ዶ/ር ሳሙኤል ሁርቃቶ – ኮሚሽነር
61. የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን – ዶ/ር መኩሪያ ሀይሌ – ኮሚሽነር