“ሁለንተናዊ ርብርብ ለትምህርት ተቋማት ደረጃ መሻሻል!”

2023-08-24T12:30:12+03:00

በሚል መሪ ቃል የ2016 የትምህርት ዘመን የትምህርት ጉባዔን አስጀምረናል። ጉባዔው የ2015 የትምህርት ዘመን ድክመትና ጥንካሬዎች የሚለዩበት፣ ትውልድን በዕውቀትና በስነ ምግባር የማነጽ ስራችን ያለበት ደረጃ የሚገመገምበት፣ ጥንካሬዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ድክመቶች ደግሞ መንስዔዎቻቸው ተለይተው የሚታረሙበት አቅጣጫ የሚቀመጥበት እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋል። በ2015 የትምህርት ዘመን ያስመዘገብናቸው የተሻሉ ውጤቶች እና ፍሬዎቻቸው ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም፣ በሰራነው እና ባሳካነው ሳንረካ ለበለጠ ድል ዝግጅት ለማድረግ ጉባዔው ጠቃሚ ሀሳቦችን እንደሚያነሳ ተስፋ አደርጋለሁ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ

“ሁለንተናዊ ርብርብ ለትምህርት ተቋማት ደረጃ መሻሻል!”2023-08-24T12:30:12+03:00

በአዲስ አበባ የሚከናወነው አዲሱ የኢንዱስትሪ መንደር ግንባታ

2022-09-16T11:59:23+03:00

የኢንዱስትሪ ፓርኩ ከ7 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በሆነ ወጪ የአነስተኛና መካከለኛ ማምረቻ የኢንዱስትሪ ልማትን ለማቀላጠፍ የሚገነባ ነው። የአምራች ኢንዱስትሪ ፓርኩን ግንባታ በ42 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት የሚያርፍ ሲሆን በውስጡም 21 የተለያየ ወለል ያላቸው ሼዶች፣ 400 የግብዓት አቅራቢዎችና ምርት መሸጫ ሱቆችም ይይዛል፡፡ ከዚህ ባለፈም 95 ሼዶችን፣ 152 የመሸጫ ሱቆችን፣ አዳዲስ ባለ አራት ፎቅ (G+4) ከፍታ ያላቸው 48 ህንፃዎች፣ ባለ ሁለት ፎቅ ከፍታ (G+2) 5 ህንፃዎች በጥቅሉ 63 የህንፃ መስሪያ ቦታዎች ከተማውን በሚመጥንና የኢንዱስትሪውን ዕድገት ባማከለ መልኩ ከዚህ በፊት ከተገነቡት የተለየ ዲዛይን ተሰርቶላቸው ይገነባሉ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ የመስሪያ ቦታዎችን ተደራሽ ለማድረግ ይበልጥ መንቀሳቀስ እንዳለበት በመወሰኑ፣ በዘንድሮ 2015 በጀት አመት በአዲስ አበባ የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ [...]

በአዲስ አበባ የሚከናወነው አዲሱ የኢንዱስትሪ መንደር ግንባታ2022-09-16T11:59:23+03:00

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በህገ-ወጥ የመሬት ወረራ የመንግስትና የህዝብን ሀብት የሆነውን ንብረት በህገወጥ መንገድ ግለሰቦች ለማስተላለፍ ሲሞክሩ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።

2022-08-26T08:20:35+03:00

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የመሬትና መሬት ነክ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን ለማስተካከል የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እየተወዱ መሆናቸው ይታወቃል። ይህን ተከትሎ ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ያሉ የመሬትና መሬት ነክ አገልግሎቶች ለጊዜው እንዲቆሙ ተደርገው የተለያዩ ማጣራቶች እየተደረጉ ይገኛሉ። በክፍለ ከተማዉ ዋነኛዉና ወሳኝ የህዝብ ጥያቄ የሆነዉን የመሬት አገልግሎት ጥያቄዎች በህጋዊ መንገድ ለመመለስ የማስተካከያ እርምጃዎች እየተወሰዱ ባለበት በዚህ ወቅት በትናንትናው ዕለት 18/12/2014 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 13 ልዩ ስሙ ምስራቅ ሎቄ (የወረዳ መሻገሪያ) በሚባል ቦታ የየካ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማት አስተዳደር ሠራተኛ የሆነች አንዲት ግለሠብ የክፍለ ከተማው ንብረት የሆነውን ጂ.ፒ.ኤስ ከአስተዳደሩ እውቅና ውጭ በመጠቀም የመንግስትና የህዝብ ንብረት የሆነውን መሬት ልኬት በመውሰድ ለግለሠብ ጥቅም [...]

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በህገ-ወጥ የመሬት ወረራ የመንግስትና የህዝብን ሀብት የሆነውን ንብረት በህገወጥ መንገድ ግለሰቦች ለማስተላለፍ ሲሞክሩ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።2022-08-26T08:20:35+03:00

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች በአፍሪካ ህብረት የልማት ኤጀንሲ (The African Union Development Agency) NEPAD ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ናርዶስ በቀለን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

2022-06-13T07:16:45+03:00

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ለአፍሪካ ህብረት የልማት ኤጀንሲ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ናርዶስ የሃገሪቱን የለውጥ እንቅስቃሴ በተለይም በመዲናዋ አዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ የለውጥና የሪፎርም ስራዎች ስላሉበት ደረጃ ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡ በተለይም በፈተናዎች ውስጥ አልፎ በርካታ የዜጎችን ህይወት የሚቀይር ፤ የከተማችንን ጎስቋላ ገፅታ የሚያድስ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ወ/ሮ ናርዶስ በቀለ በበኩላቸው በሃገሪቱ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ እንቅስቃሴ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልፀው በተመለከቱት ነገር በእጅጉ መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች ዘመናዊ የጥቁር ህዝቦች ኩራት መታሰቢያ የሆነውን የአድዋ ሙዚየምና የማዘጋጃ ቤት ህንፃ እድሳት ስራን ለወ/ሮ ናርዶስ አስጎብኝተዋል፡፡

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች በአፍሪካ ህብረት የልማት ኤጀንሲ (The African Union Development Agency) NEPAD ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ናርዶስ በቀለን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡2022-06-13T07:16:45+03:00
Go to Top